የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች ማህበር በመቀሌ እና ሽሬ እንዳስላሴ ዲስትሪክቶች በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረዉ ጦርነት ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸዉ አባል ሠራተኞች በመጀመሪያ ዙር ካደረገዉ ድጋፍ በተጨማሪ ለመጨረሻ ጊዜ በአባላት ድጋፍ መመሪያ ቁጥር 08/2012 መሠረት ሰኔ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ተጨማሪ ድጋፍ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት የመጀመሪያዉን ዙር ጨምሮ በአጠቃላይ ብር 4,657,500 (አራት ሚሊየን ስድስት መቶ ሃምሳ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ) ለወደሙት ክበባት እና ጉዳት ለደረሰባቸዉ አባላት ድጋፍ ተደርጓል፡፡ በዚህም ማሕበሩ በችግር ጊዜ ለአባላቱ ደራሽ መሆኑን አስመስክሯል።