ዉድ የባንካችን ማሕበረሰብ እና የማሕበራችን አባላት በሙሉ ስለ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች ማሕበር ከምስረታ ጀምሮ ያለዉን ታሪክ የሚገልፅ ዶክዩመንተሪይ ተዘጋጅቶ በቴሌቭዥን በሁለት ክፍል ስለሚተላለፍ እንድትከታተሉ በአክብሮት ተጋብዛችሁዋል፡፡ ዶክዩመንተሪዉ ሚተላለፍባቸዉ ቀናትና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ክፍል አንድ የሚተላለፈዉ ዛሬ ቅዳሜ 17/09/2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:30 ሰዓት በአማራ ቴሌቪዥን እሁድ 18/09/2016 ዓ.ም ምሽት 2፡30 በፋና ቴሌቪዥን የሚተላለፍ ይሆናል፡፡ ክፍል አንድን በድጋሚ ለመመልከት 19/09/2016 ዓ.ም ሰኞ ቀን 6፡00 ሰዓት በፋና ቴሌቪዥን 20/09/2016 ዓ.ም ማክሰኞ ምሽት 2፡30 በአማራ ቴሌቪዥን 20/09/2016 ዓ.ም ማክሰኞ ምሽት 1፡00 ሰዓት በEBS ቴሌቪዥን ስለሆነም ሁሉም ፕሮግራሞች የሚተላለፉት በመደበኛ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቴሌቪዥን ፕሮግራም ሰዓት ላይ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡