የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች ማህበር በባንኩ ዋና መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ አስቸኳይ እና 62ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባዉን ነሀሴ 11/2015 ዓ.ም የጀመረ ሲሆን ጉባኤዉም ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ ታዉቋል፡፡ ምክር ቤቱ በሁለት ቀናት ቆይታዉ፡- 1ኛ.በወቅታዊ የሠራተኞች ጥያቄዎች 2ኛ.በአጠቃላይ ምርጫ አካሄድ እንዲሁም የ2015 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ዝርዝር ሪፖርት እና የ2016 በጀት ዓመት እቅድ ዙሪያ ተወያይቶ ዉሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡