በአለም አቀፍ ደረጃ ለ36ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ35ኛ ጊዜ የተከበረዉን የአለም አቀፍ የኤድስ ቀንን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የትዉልድህን አድን ፀረ ኤድስ ኮሚቴ እና የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) በጋራ በመሆን በዛሬዉ ዕለት ማለትም ህዳር 25 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲሱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ‹‹የማህበረሰብ መሪነት ለላቀ ኤች.አይ.ቪ መከላከል›› በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡ በዕለቱም ከባንኩ የተወከሉ፣ አመራሮች ከኢሰማኮ፤ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር እንዲሁም የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በመድረኩ ላይም የተለያዩ ትምህርታዊ እና ነባራዊ ሁኔታዎች ቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡