ማሕበራችን በፋይናንስ ተቋማት ኢንዱስትሪ ፌደሬሽን ስር ለታቀፉ አቻ ማሕበራት ታህሳስ 11 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መ/ቤት በሚገኘዉ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የልምድ ልዉዉጥ እና ተሞክሮ በስልጠና መልክ አጋርቷል፡፡በእለቱም በባንኩ ባለሙያዎች የበለፀገዉ የማሕበራችን ድህረ-ገፅ (Web-Site) እና የመረጃ ቋት (Database) የባንካችን የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል፡፡ ከአቻ ማሕበራት የመጡ እንግዶችም በማሕበራችን አዲሱ ቢሮ በመገኘት እየተሰራ ያለዉን ስራ በአካል በመገኘት ጎብኝተዋል ገለፃና ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል፡፡ በመጨረሻም የኢትዮጵያ ፋይናንስ ተቋማት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት አቻ ማሕበራት የተጀመረዉን ግንኙነት ማጠናከር እንዳለባቸዉ አሳስበዉ ልምድ ልዉዉጡ ተጠናቋል:: የማሕበራችን ድህረ-ገፅ (Web-Site) :- https://cbetradeunion.cbe.com.et