የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰራተኞች ማሕበር 63ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ ማከሄድ ጀመረ። በስብሰባው መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሰው ሃይል አስተዳደር ምክትል ፕረዚዳንት አቶ ኤፍሬም መኩርያ እና የፋይናንስ ተቋማት ሰራተኞች ማሕበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ፕረዚዳንት አቶ ደስተ በርሀ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። ከጧት በነበረው ስብሰባ ክፍለ ጊዜ የስድስት ወር የስራ አስፈፃሚ ሪፖርት እና ኦዲት ሪፖርት ቀርቦ ከምክር ቤቱም ጥያቄ ተነስቶ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ ፀድቋል። ስብሰባው ከሰዓትም የሚቀጥል ሲሆን ቀጥሎ ያለውን መረጃ ተከታትለን የምናደርስ ይሆናል።