2176 0906570000 tradeunion@cbe.com.et

News

ዉይይት ተካሄደ

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ 32 አባላትን የያዘ በተከበሩ ፕሮፌሰር መሀመድ አብዱ ሰብሳቢነት የተመራ ልኡክ ከባንካችን ፕሬዝዳንት እና የማኔጅመነት አባላት እንዲሁም የማህበራችን ስራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት ዉይይት ተደርጓል፡፡ በዉይይቱም የተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች፡-የ6 ወር የባንኩ አፈፃፀም ዙሪያ ፤በባንኩ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ፤በባንኩ የብድር አሰጣጥ ዙሪያ ፤በሰራተኛዉ ቅጥር ፤ዝዉዉር እና ሌሎችም አንኳር ጉዳዮች ጥያቄ ተነስቶ ሰፊ ዉይይት ተደርጓል፡፡ በእለቱ ማህበራችን የተገኘዉን እድል በመጠቀም ለተወካዮች ምክር ቤት ልዑካን -ስለማህበራችን ታሪካዊ ዳራ በጥቂቱ ገለፃ ተደርጎላቸዋል -ማህበራችን ከባንኩ ጋር ስላለዉ መልካም ግንኙነትና ተግዳሮቶች ገለፃ ተደርጎላቸዋል በመጨረሻም ለተከበረዉ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ልዑክ ማህበራችን ካነሳቸዉ ጥያቄዎች ዉስጥ በጥቂቱ -ከ Tax ጋር ተያይዞ ያለዉን ጉዳይ አፅንኦት እንዲሰጡ -በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች ሰራተኞቻችን ደህንነታቸዉ አደጋ ዉስጥ ሆኖ በጦርነት መካከል በመሆን እያገለገሉ ያሉ ሰራተኞቻችን ደህንነታቸዉ እንዲጠበቅ መንግስት የበኩሉን እንዲወጣ ተጠይቋል፡፡ -መንግስት ለንግድ ባንክ ልዩ ትኩረትና ድጋፍ ማድረግ እንዳለበት ከተነሱ ጥያቄዎች ጥቂቶቹ ሲሆኑ እነዚህ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ዉይይት ከተደረገ በኋላ ሰራተኛዉ የአገልግሎት አሰጣጡን ማዘመን እንዳለበት አፅንኦት በመስጠት የእለቱ ስብሰባ ተጠናቋል፡፡

0 Comments

Leave A Comment

Get In Touch

2176

tradeunion@cbe.com.et

0906570000